ኢትዮጵያ፤ የእርሻ ልማትና የምግብ ብቃት

በአሁኑ ጊዜ በአፍሪቃ፤ በተለይም በአፍሪቃ ቀንድ አካባቢ ላይ ላተኮረ በዓይን ላይ የሚደቀነው የተለመደው የረሃብ አስከፊ ገጽታ ነው። የአካባቢው 12 ሚሊዮን ሕዝብ በወቅቱ የረሃብ ሞት አደጋ ተደቅኖበት የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያም የድርቅ መለያነት ባለበት ቀጥሏል።