ሶሪያ፣ አሜሪካ፣ አውሮፓና ኢትዮጵያ

እስክንድር ነጋ – (አዲስ አበባ)

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ሰሞኑን ተወጥረው ሰነባብተዋል፡፡ የመንግሥታቸው ወጪ ከገቢው መንጥቆ ማምለጡ አዲስ ዜና አይደለም፡፡ ትንሹ ቡሽ እንደ ... 2ዐዐዐ . ከክሊንተን ስልጣን ሲረከቡ፣ የአሜሪካ መንግሥት በካዝናው ትርፍ ገንዘብ ነበረው፡፡ ገቢው ከወጪው ይበልጥ ነበር፡፡ 21ዐ፣ ዓመታዊ የባጀት ጉድለቱ 1 ትሪሊዮን ዶላር በላይ ሄዷል፡፡ በየዓመቱ የተጠራቀመው ጉድለትና ብድር ተደማምሮ ዘንድሮ 14 ትሪሊዮን ዶላር በላይ አሻቅቧል፡፡ ይሄ ነው ብሔራዊ ዕዳ ማለት፡፡ ሸክሙ አሜሪካን እያንገዳገዳት ነው፡፡