የጀርመን መንግሥት የአስካሉካንን ባለቤት አሳልፎ ሰጠ

በአፍሪካ አኅጉር ለመጀመሪያ ጊዜ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 19ኛው የዓለም ዋንጫ ከኢትዮጵያ ተመልካቾችን ለመላክ ተብሎ በተፈጠረ ማጭበርበር ምክንያት፣ ከህዳር 3 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ በጀርመን ፖሊስ ቁጥጥር ሥር የነበሩት የአስካሉካን ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ባለቤት ለኢትዮጵያ ተላልፈው ተሰጡ፡፡