ሐምሌ ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ድርጊቱ የተፈጸመው ንብረትነቱ የቱርክ የሆነና በጥጥ ማምረት ስራ ላይ የተሰማራውን የቶረን የእርሻ ኩባንያ ገንዘብ ጭኖ በመጓዝ ላይ ባለ መኪና ላይ ነው። የኩባንያው ሃላፊዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአሜሪካ ዶላርና ብር ይዘው በ7 የልዩ ሃይል ፖሊስ አባላት ታጅበው ወደ ወንዶ ጎጊ ወረዳ በሚጓዝበት ወቅት፣ አንደኛው …

ሐምሌ ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ወኪላችን እንደገለጸው ከሁለት ሳምንት በፊት በአርባምንጭ ከተማ ሊደረግ የታቀደው የተቃውሞ ሰልፍ በገዢው ሃይል የጸጥታ አባላት እንዲበተን ከተደረገ በሁዋላ፣ ከ120 በላይ ሰዎች ተይዘው በአርባምንጭ እስር ቤት ታስረዋል። አንድ የገዢው ፓርቲ ደጋፊ የሆነ ሰው የጋሞን ብሄረሰብ ታሪክ አንቋሾ መጽሄት አሳትሟል በሚል የተጀመረው ተቃውሞ እየጨመረ መሄዱን ተከትሎ፣ …

ሐምሌ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አሜሪካዊው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ” ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ …

ሐምሌ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሀምሌ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጎንደር ከተማ ውስጥ በፖሊስና ደህንነቶች ታፍኖ የተወሰደው የሰማያዊ ፓርቲ አባል መምህር አለላቸው አታለለ የት እንደሚገኝና በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳለ ለማወቅ እንዳልቻሉና ከፍተኛ ጭንቀት ላይ መሆናቸውን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል በጎንደር መምህራን ኮሌጅ የአይ ሲቲ መምህርና የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ የሆነው መምህር አለላቸው አታለለ …

ሐምሌ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዊክሊክስ ባወጣው መረጃ ላይ የኢትዮያና የኬንያ ገዢዎች ሶማሊያን ለአራት ቦታ በመክፈል ለመቀራመት በሚስጥር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስነብቧል። ሶማሊያ ለም እና በማዕድን የበለጸገ ምድር ባለቤት በመሆንዋ የብዙ ሀገራትን ፍላጎትን ትስባለች።ዊክሊክስ ጅቡቲ ከሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኤንባሲ መረጃውን እንዳገኘው ገልጿል።በአሁኑ ወቅት ብዙ አገራት በሶማሊያ ውስጥ ይገኛሉ፤የተወሰኑት በግፊት እንዲወጡ ተደርገዋል …

ኢሳት ዜና (ሃምሌ 16, 2007) የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ወደ አዲስ አበባ ከተማ በሚገቡ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ተንቀሳቅሳችኋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች በእስር ቤት ድብደባ እየተፈጸመባቸው እንደሆነ ለፍርድ ቤት ገለጹ። ሐሙስ እለት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አቶ መርከቡ ሀይሌና አቶ አበበ ቁምላቸው ፕሬዘዳንት ኦባማ ወደ ሀገሪቱ በሚመጡ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ …

ሐምሌ ፲፸ (አስራሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ግንባሩ ባወጣው መግለጫ “በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል።” ብሎአል። አርበኞች ግንቦት 7 “በቅርቡ የጀመረው የነፃነት ትግል የፈጠረበት መደናገጥ ለመሸፈንና ንቅናቄውን በኢትዮጵያ ሕዝብና በዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብ ለማስወገዝ ያግዘኛል ብሎ ያመነበት ይህን ዘግናኝ ሴራ ከሳምንት በፊት …

ሐምሌ ፲፸ (አስራሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ ፈንታሁን ታደሰና ሌሎች 6 እስረኞች ለ5 ወራት ያህል ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። በፖሊስ የካቲት 21 ቀን 2007 ዓ.ም. የታሰሩት እነ አቶ ፈንታሁን በወቅቱ የጉሃላ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ወስዷቸው የነበር ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ”እኛ ይህን ጉዳይ አናይም! ከፈለጋችሁ ወደ ዞን ፍርድ ቤት ወስዳችሁ …

ሐምሌ ፲፸ (አስራሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የድርጅቱ የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሚስ ሌስሊ ሌፍኮ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብአዊ መብት ጥሰት የፕሬዚዳንቱ አንድ አጀንዳ ይሆናል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ። ፕ/ት ኦባማ ኢትዮጵያን መጎብኘት አልነበረባቸውም የሚለው አስተያየት ዋናው ጉዳይ አለመሆኑን የገለጹት ሌፍኮው፣ ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ የሚለው ጥያቄ ዋናው …

ሐምሌ ፲፮ (አስራስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ጥያቄውን ያቀረቡት በአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ግንኙነት የተዘዋዋሪ ወንጀሎችና የሕዝብ ደሕንነት ሊቀመንበር የሆኑት ሴናተር ማርኮ ሩቢዮ ናቸው። ዴሞክራሲ፣የሰብዓዊ መብትና ዓለምአቀፍ የሴቶች ጉዳይ፣ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ወቅት ቅድሚያ ሊሰጡባቸው የሚገቡ አንገብጋቢ ጉዳዮች መሆናቸውን ሴናተሩ ጠቅሰዋል። ሴናተር ማርኮ ሩቢዮ ”ኢትዮጵያና አሜሪካ ሽብርተኝነትን በመዋጋት በአካባቢው መረጋጋትን …

ሐምሌ ፲፮ (አስራስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሽብርተኝነት ተከሶ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘው በአርባ ምንጭ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ ዋና ፀኃፊ አቶ በፍቃዱ አበበ በትናንትናው ዕለት ሀምሌ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት የመከላከያ ምስክሮቹን አሰምቷል፡፡ ከአምስቱ የመከላከያ ምስክሮች መካከል አራቱ ፣ የአርባ ምንጭ ፖሊስና ደህንነቶች በፍቃዱ አበበ ላይ በሀሰት …

ሐምሌ ፲፮ (አስራስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በክልሉ በሚገኙ በሁሉም አካባቢዎች 38 ብር ይሸጥ የነበረው አንድ ኪሎ በርበሬ ፣ 185 ብር በመሸጥ ላይ ሲሆን፣ 26 ብር በኪሎ ይሸጥ የነበረው ምስር ደግሞ ከ50 ብር በላይ እየተሸጠ ነው። በተፈጠረው የዋጋ ንረት የክልሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው። ክልሉ በበልግ ወራት የተጠበቀው የምስር ምርት ባለመገኘቱ የተፈጠረ ነው …

ሐምሌ ፲፮ (አስራስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በማላዊ ካሮንጎ ከተማ አቅራቢያ 34 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። ማንነቱ ያልታወቀ ማላዋዊ ሕገወጥ ስደተኞችን አስተላላፊ ግለሰብ ”በሙያው የካበተ ልምድ አለኝ፤ከዚህ በፊት ከማላዊ፣ዛምቢያ፣ሞዛምቢክና ዝምባቢዌ ስደተኞችን አሸጋግራለሁ።” በማለት ስደተኞችን አጭበርብሮ በማሳመን 3 ሚልዮን የማላዊ ክዋቻ ተቀብሏቸዋል።የካሮንጋ የስደተኞች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ …

ኢሳት ዜና (ሃምሌ 13 2007 አም) የበክኔል ዩኒቭርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑትና በቅርቡ ከዚሁ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማእረግ የተቀበሉት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሳምንቱ መጨረሻ ኤርትራ መግባታቸው በኢትዮጵያውያን ዘንድ አብይ መነጋገሪያ ሆኖ ወጥቷል ፤ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የመሪውን ትግል ቦታ መሄድ ይፋ በማድረግ ኢትዮጵያውያን በአቅማቸው መጠን በትግሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። “እነሆ የአርበኞች ግንቦት ሰባት …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ድርጅቶቹ ለፕ/ት ኦባማ በጻፉት ደብዳቤ ኬንያና ኢትዮጵያ በብሄራዊ ደህንነት ስም የሚያደርሱት የሰብአዊ መብት ረገጣ ፣ አለማቀፍ ህግጋትን መጣስ ብቻ ሳይሆን፣ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የሚደረገውን ጥረት አደጋ ውስጥ እንደሚጥለው ገልጸዋል። ደብዳቤውን የጻፉት፣ አትላንታ ካውንስል፣ ካውንስል ኦን ፎሬን ሪሌሽን፣ ሂውማን ራይትስ ፈርስት፣ ከኒይ ግራጅዌት ሴንተር እና ሲቲ ኮሌጅ ኦፍ …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲቀርቡ ሲል የልደታ ፍርድ ቤት 19 ኛው የወንጀል ችሎት ወሰነ፡፡የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በምስክርነት እንዲያቀርብ ሲል ፍርድ ቤቱ ለሀምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥትዋል። አቶ አንዳርጋቸው …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዓለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይ ኦ ኤም በየመን አድርገው በሕገወጥ መንገድ ወደ ሳኡዲ አረቢያ ለመግባት ሲሞክሩ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ታግተው የአካልና የሞራል ጉዳት የደረሰባቸውን ቁጥራቸው 3 ሺ 478 የሚሆኑ በጎፈቃደኛ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው መመለሱን አስታውቀዋል። የ18 ዓመቱ ወጣት አልማይ ፍፁም ”በመኪና ተጭነን ወደ ሳዑዲ ድንበር እንደተቃረብን …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉት አቶ ጌታሁን ካሳ ”የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም ሚናውና የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ላይ ይጋጠሙት ፈተናዎች” በተሰኘ ጥናታዊ የምርምር ሥራቸው ላይ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተቋም ነፃና ገለልተኛ ሆኖ፣ የሕግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አኳያ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል ማለት እንደማይቻል አመልክተዋል፡፡አቶ …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት እንደ አዲስ ባገረሸው የምስራቅ እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና የሃረሪ ክልል ፖሊሶች ግጭት 4 ፖሊሶች በመከላከያ አባላት ታፍነው መወደሳቸውንና እስካሁን የደረሱበት አለመታወቅን የሃረር ወኪላችን ገልጿል። የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ከሁለቱ ሃይሎች የተውጣጡ መሪዎችን ለማነጋገር ሙከራ ቢያደርጉም አልተሳካላቸውም። በሃረሪ ፖሊስና በምስራቅ እዝ የፖሊስ አባላት መካከል ያለው ግጭት …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርባምንጭ ምንጮች እንደገለጹት ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፌደራል ፖሊስ አባላት በየአንዳንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ፍተሻ ሲያደርጉ የታየ ሲሆን፣ አንዳንድ ሰዎች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጣቸው መልስ ” ግንቦት7″ ከተማው ውስጥ ገብቷል የሚል ነው። በከተማውና በዙሪያ ወራዳዎች የሚታየው ፍተሻና ቁጥጥር መጨመሩን ፣ ህዝቡም ግራ ተጋብቶ እንደሚገን ምንጮች …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ከ1 እስከ 6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሽ ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው አቶ ተማም አባቡልጉ ተከሳሾቹ ሀምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኦባማ በአፍሪካ ለሚያደርጉት ጉዞ በተለይ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው አገሪቱ በሰብአዊ መብት ጥሰቶችና በዲሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር የሌላት በመሆኑ ከዓለምአቀፍ ማኅበረሰቡ ኢትዮጵያን መጎብኘት ማቆም እንዳለባቸው በማሳሰብ ከፍተኛ ወቀሳ እየተሰነዘረባቸው ነው። በአፍሪካ ስላለው የሰብዓዊመብት አያያዝ ላይ ፕሬዝዳንቱ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል።በአንፃሩ ለፀጥታና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ዓላማ ይዘው ወደ አፍሪካ አህጉር የሚያቀኑት ኦባማ …

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “ለነጻነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል መሬት ላይ ወርዶ መምራት ይገባል” በሚል እምነት በከፍተኛ ውጣ ውረድ ከአሜሪካ ኤርትራ መግባታቸው እንደተሰማ በአርበኞች ግንቦት7 ሰራዊት ውስጥ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ፣ አስመራ በሚገኘው የድርጅቱ ጽህፈት ቤት አቀባበል ያደረጉላቸው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ ተናግረዋል።በዋና ጽህፈት …

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ህውሃት 40ኛ ዓመቱንና ኦህዴድ 25ተኛ አመቱን ባከበሩበት ማግስት፣ ብአዴንም 35ተኛ አመቱን ከሁለቱ ድርጅቶች ባላነሰ ለማክበር በብዙ መቶ ሚሊዮን ብር የሚቆጠር ገንዘብ መመደቡን የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ዝግ ስብሰባ መነጋገራቸውን ምንጮች ጠቅሰዋል። ከሀምሌ ወር, 2007 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም ጋዜጠኛ የብአዴንን ታሪክ ለማወቅ የሚረዱትን መጽሃፍት በማሰባሰብ እንዲያነብና …

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን ሐምሌ 13/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። በእስር ላይ የሚገኙት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አቤል ዋበላ ለ31ኛ ጊዜ ፍርድ …

ሐምሌ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመላው አለም የሚኖሩ ሙስሊሞች 1 ሺ 436ኛውን የኢድ አልፈጥር በአል አክበረዋል። በአሉ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተከበረ ሲሆን፣ ካለፉት 3 ዓመታት ጀምሮ ሲታይ እንደነበረው በአካባቢው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፌደራል ፖሊስ ታይቷል። በተለያዩ አለም ክፍሎች በአሉ በአንጻራዊ መልኩ በሰላም ሲጠናቀቅ፣ በናይጀሪያ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ ከ10 ያላነሱ ሰዎች መገደላቸውን …

ሐምሌ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት ችግሩ የተፈጠረው በጋሞና በጎፋ ተወላጅ ባለስልጣኖች መካካል ነው። የዞኑን፣ የክልሉንና የፌደራል ስልጣኑን የተቆጣጠሩት የጎፋ ተወላጅ ባለስልጣኖች፣ ጋሞዎችን ሰድበዋል ፣ የጋሞ ተወላጅ ባለስልጣናትን በንቀት ያያሉ በሚል እርስ በርስ በጀመሩት ቁርሾ፣ የመንግስት ስራ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ የእርስ በርስ ሽኩቻውን ወደ ህዝብ በመውሰድ የጋሞ ባለስልጣናት የጋሞ …

ሐምሌ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሴንተር ፎር ስትራቴጂክ ኤንድ ኢንተርናሽናል ስተዲስ የተባለው ተቋም ” ከአሜሪካ ጉዞ በፊት የአሜሪካ ፖሊሲ በኬንያና በኢትዮጵያ” በሚል ርእስ ባዘጋጀው ፓናል ውይይት ላይ የተገኙት በጆርጅ ማሶን ዩኒቨርስቲ የግጭት አስወጋጅ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ቴሬንስ ሊዮንስ እንደተናገሩት ኢህአዴግ በቅርቡ በኤርትራ ላይ ጦርነት ለማወጅ የሰጠውን መግለጫ አሜሪካ እንደማትደግፈውና እንደማትተባበር በግልጽ …

ሐምሌ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በበሳውዲ አረቢያ ለረዢም ጊዜ በስደት ቆይተው ወደ ትውልድ ቀያቸው የተመለሱ በአማራ ክልል የሚገኙ ከስደት ተመላሾች ፤በራሳቸው ካፒታል እና ጥረት ለመንቀሳስ ቢሞክሩም “ልዩ ልዩ መሰናክል በመፍጠር የገዢው መንግስት ሊያሰራን አልቻልንም “በማለት ተናግረዋል፡፡‹‹ ከስደት ከተመለስን በኋላ በማህበር ተደራጁ በማለት ቢያደራጁንም የምንሰራበት የእርሻ መሬት ለማግኘት ለአምስት ወራት አሰቃይተውናል፡፡ ›› …

ሐምሌ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምርጫ 2007ትን መቶ በመቶ በሆነ ድምጽ አሸንፊያለሁ ብሎ ያወጀው ኢህአዴግ፣ ከምርጫው በሁዋላ ያሰባሰበው የህዝብ አስተያየት ለፓርቲውም ሆነ ለአገሪቱ ህልውና አስፈሪ መልእክት የያዘ ነው ሲል ድምዳሜ ላይ ደርሷል። ሪፖርቱ በመጪው ነሃሴ በሚካሄደው የግንባሩ ጉባኤ ላይ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። ህዝቡ በአስተዳዳር፣ በፍትህ፣ በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች፣ በውሃና በመብራት እጦት …

ኢሳት ዜና (ሃምሌ 9 2007) ግጭት ወደአለበት የመን የሚሰደዱ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ አሳስቦት እንደሚገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ትናንት ረቡእ ገለጸ ። በየመን ያለው የጸጥታ ሁኔታ አደገኛ ቢሆንም በብዙ ሺ  የሚቆጠሩት ስደተኞች አሁንም ድረስ ወደ ሀገሪቱ እየገቡ መሆናቸውን ረቡእ ከጄኔቫ በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ የሰጡ የደርጅቱ ሀላፊዎች አስታውቀዋል። ከኢትዮጵያኑ በተጨማሪ የሶማሊያ ተወላጆች ወደየመን እየተሰደዱ እንደሆነ የገለጸው የተባበሩት መንግስታት …

ሐምሌ ፺፻ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በገዢው መንግስት ከፍተኛ አፈና የሚደርስበት የኢሳት የቴሌቪዝን ስርጭት ከሳምንታት ሙከራ በሁዋላ ዛሬ ሙሉ ስርችቱን በ ኤም 44 ሳተላይት ጀምሯል። አዲሱ ሳተላይት ጠንካራ ሲግናል ያለው ቢሆንም፣ ገዢው ፓርቲ በሙከራው ወቅት ስርጭቱን ለማፈን ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱን የኩባንያው ኢንጂነሮች ገልጸዋል። ተመልካቾች አልፎ አልፎ የድምጽ ወይም የምስል መዛባት ቢያጋጥማቸው …

ሐምሌ ፺፻ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሰማያዊ ፓርቲ ሊ/መንበር ኢንጂነር ይልቃል የፓርቲያችሁ አባሎች የትጥቅ ትግልን ሊቀላቀሉ ሲሄዱ ተይዘዋል በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ በመርህ ደረጃ ኢህአዴግን ብሶት ከወለደው ሰው ጠመንጃ የማያነሳው ለምን ድነው ሲሉ ጠይቀዋል። ሰው መኖር ካልቻለ ምን አማራጭ አለ ሲሉ የጠየቁት ኢ/ር ይልቃል ሰው መቀመጫ መሄጃ ሲያጣ ቢሀድ ምን ይገርማል፣ አትሂድስ …

ሐምሌ ፺፻ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ቀደም ብሎ እንደተዘገበው በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እስረኞች ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችሁዋል ከተባልን፣ አቶ አንዳርጋቸው ቀርበው ይጠየቁልን የሚል መከላከያ መልስ ሰጥተው ነበር። ፍርድ ቤቱ አቶ …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ፣ የቀዳሚ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅና የሚሊዮኖች ድምጽ ጋዜጣ ሪፖርተር የነበረው ሃብታሙ ምናለ ” የአልሸባብ የሽብር ወንጀል ቡድን ሴል ነህ” በሚል ተጠርጥሮ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው አምቼ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደሚገኝ ገልጿል። ሃብታሙ፣ “የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሚገኙበት ስብሰባ ላይ …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ሰሜናዊ ምዕራብ 302 ኪሎ ሜርት ‘ርቀት ላይ በሚገኘው በዋጅድ አውራጃ ልዩ ስሙ ቦቆል ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ማክሰኞ ዕለት የጦር መሳሪያ ያነገቡ የኢትዮጵያ ወታደሮችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች በከተማዎች ውስጥ ሲርመሰመሱ መታየታቸውን የዘገበው ሆርስድ ሚዲያ፣ በወታደሮቹ ላይ ጥቃት ለመፈጸም የሞከሩ 7 ወታደሮች መገደላቸውን የሰድሩ አውራጃ …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ የሁለተኛው ዙር የትራንስፎርሜሽን እቅዱን እያስታወቀ ባለበት ቢዘህ ወቅት ከህዝቡ በርካታ አቤቱታዎችን እያስተናገደ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን እና አቶ በረከት ስምኦን በመሩት ፤ የእንጅባራ ፤ ወልድያ እና ቻግኒ ከተሞች ስብሰባ ፣ ህዝቡ “ኢህአዴግ ለወጣቱ መልካም አማራጮችን አለማቅረቡን እንዲሁም በውሃ ና በመብራት ችግር እየተሰቃየ መሆኑን” …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሃምሳ በላይ የሚሆኑ የአፍሪካና የዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጓቾች ኅብረት ማክሰኞ ዕለት ባወጡት የአቋም መግለጫ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በያዝነው ወር በሚያደርጉት የአፍሪካ ጉብኝታቸው ወቅት ከዴሞክራሲ መብት ተሟጓቾች ጋር ፊትለፊት መገናኘት እንዳለባቸው አሳሰቡ። የሰብዓዊመብት ኅብረት ለሁዋይት ሃውስ በላኩት ደብዳቤ ላይ ባራክ ኦባማ በኢትዮጵያና በኬንያ ያለውን የመብት ጥሰቶች ሊመለከቱዋቸው …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዴይሊ ኔሽን እንደዘገበው ኢትዮጰያውያኑ በምራባዊ የሀገሪቱ ግዛት በኢምቡ ክፍለ -ከተማ በኪቲሙ ገበያ አቅራቢያ በሚገኝ እርሻ ውስጥ ሊደበቁ ሲሞክሩ ነው የተያዙት። ሁሉም ወንዶችና ከ30 ዓመት በታች የሆኑት ኢትዮጰያውያን ባካባቢው ነዋሪዎች ጥቆማ በበቆሎ ማሳ ውስጥ እንዳሉ መያዛቸውን የገለጹት የኢምቡ ኮሚሽነር፤ ሁሉም የኪስዋሀሊ ቋንቋን እንደማያውቁ አመልክተዋል። በ አካባቢው ህገወጥ …

ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ውስጥ በመለስተኛ የግል የአውሮፕላን የበረራ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ባቀረቡት አቤቱታ፣ የስራ ዘርፉ ከቢሮክራሲ ጋር በተያያዘ ለኪሳራ እየዳረጋቸው መሆኑን ሳያንስ፣ ከበረራው 24 ሰአታት በፊት ለመከላከያ ሚኒስቴር ሪፖርት እንዲያደርጉ መታዘዛቸው ስራቸውን አስቸጋሪ አድርጎታል። አንዳንድ ባለሀብቶች በተለይ ወደ ሰሜን የአገሪቱ ክፍል የሚደረገው በረራ ፈታኝ እንደሆነባቸው ገልጸዋል። አስቸኳይና …

ሐምሌ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሁለተኛውን የኢህአዴግ መንግስት የ5 አመታት የመከላከያ ሰራዊት እቅድ በተመለከተ በቤተመንግስት በተካሄደው ስብሰባ ላይ ኢህአዴግ አሁን ያለውን ወታደራዊ አቅምና በሚቀጥሉት አምስት አመታት የሚያስፈልጉትን የጦር መሳሪያዎች በጄ/ል ሳሞራ የኑስ በኩል ዘርዝሮ ያቀረበ ሲሆን፣ በዚህ ሪፖርት ወቅት ባለፉት 5 አመታት ወደ ቻይና ፣ ኮሪያ ፣ ጃፓን እና እስራኤል ለወታደራዊ …

ሐምሌ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት ኢህአዴግ የጅቡቲ አፋር እና የኤርትራ አፋር ተቃዋሚዎችን በማሰባሰብ የኤርትራ መንግስት ተቃዋሚ የታጠቁ ሀይሎች በሚል የቀጥታ የመሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ምንጮች ገልጸዋል። ሰልጣኞቹ አስመራ ድረስ በመሄድ ስልጣን እንደሚይዙ ተስፋ ተሰጥቷቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚኖሩ የኤርትራ ስደተኞች ወደ ትግሉ እንዲቀላቀሉ ጨና እያሳደረ እንደሚገኝም የኢሳት ምንጮች …

ሐምሌ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው ሐምሌ 7 ቀን 2007 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሀገራዊ ‹‹የውሸት ምርጫ›› ከተጠናቀቀበት ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም ማግስት በምርጫው በንቃት ይሳተፉ የነበሩና በአስተሳሰባቸው በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን ዜጎች በማንአለብኝነት መደብደብ፣ ከሰራ ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማሸማቀቅና መግደል የአገዛዙ ዋና መገለጫ ሆኗል” ብሎአል። ይህንን ድርጊቱን ገዥው ፓርቲ በአስቸኳይ …

ሐምሌ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አዲስ ስታንዳርድ እንደዘገበው አክሽን ኤይድ በካናዳ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ ህብረት ይሽከረከራሉ ያላቸውን 77 ሀገሮችን የአዲስ አበባው ጉባዔ አላማ እንዳይሳካ እንቅፋት እየፈጠሩ ነው ሲል ተቃውሞ አቅርቧል። የድርጅቱ ኃላፊ አዲያምኖ ካምፖሊና የበለጸጉት ሀገሮች ጥቂት ሀብታም ሀገሮች የበለጠ ሀብታም ፤ብዙሀኑ ደሀ ሀገሮች ደግሞ ይበልጥ እንዲደኸዩ እየሠሩ ነው ሲሉም ከሰዋል። አሁንም …

ኢሳት ዜና (ሐምሌ 6 2007) የኢትዮጵያ መንግስት ከጣሊያኑ የሳይበር ሴኩሪቲ ኩባኒያ ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ሲገልጽ ቢቆይም የኩባኒያው ሀላፊዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ትናንት ሰኞ ማረጋገጫ መስጠታቸውን የእንግሊዙ ዘጋርዲያን ጋዜጣ ዘገበ። የሀኪንግ ቲሙ መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ዴቪድ ቭንሴንዜቲ ድርጅታቸው ኢትዮጵያን ጨምሮ ለግብጽ ለሱዳንና ለሞሮኮ የአፍሪካ ሀገራት አገልግሎቱን ሲያቀርብ መቆየቱን የፋ አድርጓል። “ኢትዮጵያ አገልግሎታቸንን ጋዜጠኞችንና የመንግስት ተቃዋሚዎችን …

ሐምሌ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መድረክ ባወጣው መግለጫ ከ2007 ምርጫ በሁዋላ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የተገደሉ የመድረክ አባላት ቁጥር 5 ደርሷል። የኢህአዴግ አገዛዝ በደቡብና ኦሮምያ የሚፈጽማቸው ድብደባዎችና እስራቶች መጨመራቸውንም መድረክ ገልጿል። በከፋ ዞን በግንቦ ወረዳ በአድዮ ካካ ምርጫ ክልል በጎጀብ ምርጫ ጣቢያ የመድረክ ምርጫ ታዛቢ/ወኪል ሆነው የሠሩት አቶ አሥራት ኃይሌ ማንነታቸው ባልታወቁ …

ሐምሌ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ሰሞኑን በአርበኞች ግንቦት7 እና በገዢው ፓርቲ ወታደሮች መካከል የተደረገውን ጦርነት ተከትሎ በዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ የሚመራው የምርት ገበያ ድርጅቱ በመተማና አብርሃ ጅራ የሚገኙ ቅርንጫፎቹን በመዝጋት ወደ ጎንደር ከተማ ለማዛወር እቅድ እንዳለው ምንጮች ገልጸዋል። ድርጅቱ በሰሜን አካባቢ በሁመራ፣ ጎንደርና መተማ ለሰሊጥ ጥራት ምደባና ማከማቻ …

ሐምሌ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመናገሻ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ሀምሌ 3/2007 ዓ.ም በደህንነትና ፖሊሶች ተይዞ የታሰረውን የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ደብሬ አሸናፊንና በወቅቱ ከእሱ ጋር ተይዘው የታሰሩትን ወጣቶች ጉዳይ እንደማያይ አስታውቋል፡፡ ዛሬ ሀምሌ 6/2007 ዓ.ም ደብሬ አሸናፊ፣ ቴዎድሮስ ሻንካና ኤፍሬም የተባሉት ታሳሪዎች አምስት ኪሎ በሚገኘው የመናገሻ ፍርድ …

ሐምሌ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በርካታ ፖሊሶችና የታጠቁ ኃይሎች በመኪና በመሆን ከተማዋን ሲዞሩ መዋላቸውን ዘጋቢያችን ገልጻለች። የፖሊስ አባላት በተጠንቀቅ (stand by) ሆነው እዲጠብቱ የታዘዙ ሲሆን፣ ከአሁን በፊት ለምርጫ ቅስቀሳ በሚል ለባለ ይዞታ ቦታ ባለቤቶች የተሰጠው ጊዜያዊ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ ከተቀማ በሁዋላ፣ ዛሬ ደግሞ ይባስ ብሎ አንዳንድ ቤቶችን በግዳጅ እያፈረሱ ነው። ህብረተሰቡ …

ሐምሌ ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት የአርበኞች ግንቦት7 በወሰደው ፈጣን ጥቃት በርካታ የኢህአዴግ ወታደሮች መገደላቸውን ፣ ይህንን ተከትሎ የወልቃይትና አካባቢው ህዝብ ያሳያው ድጋፍ እና ሽምቅ ተዋጊዎችን ለመቀላቀል የሚጠይቀው ወጣት መበራከት ያሰጋው ገዢው ፓርቲ፣ የአየር ሃይል አባላት በጠጠንቀቅ እንዲቆሙ ማዘዙን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የአየር ሃይል አባላቱ ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ ቅዳሜና …