በአፍሪቃ ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች

በአፍሪቃ በህፃናት ላይ የሚካሄድ ወሲባዊ ንግድ እንዲገታ ህብረተሰቡና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ተጠየቁ ። በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ በተካሄደ ስብሰባ ላይ እንደተገለፀው በአፍሪቃ በሚሊዮች የሚቆጠሩ ወጣቶችና ህፃናት የወሲብ ንግድ ሰለባ ናቸው ።