ሃገራቸውን ጥለው በሚሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር ኢትዮጵያ የቀዳሚነቱን ስፍራ ያዘች
በአህጽሮተ ቃሉ ሲፒጄ በመባል የሚጠራው አለም አቀፉ የጋዜጠኛች መብት ተንከባካቢ ድርጅት በትናንትናው እለት ይፋ ባደረገው ሪፖርት እንደገለጸው እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር ከ2001 እስከ 2011 ባለው ጊዜ ውስጥ በዓለማችን አገራቸውን ጥለው ወደ ሌሎች አገሮች በሚሰደዱ ጋዜጠኛች ቁጥር ኢትዮጵያ አንደኛ መሆኗን አስታወቀ።
ስፒጄ የጋዜጠኞችን ስደት አስመልክቶ አገሮችን በደረጃ ሲያስቀምጥ ከኢትዮጵያ 79፤ ከሶልማሊያ 68 ፤ከኢራን 66 ፤ ከኢራቅ 55 ፤ከዚምባብዌ 49፤ ከኤርትራ 47፤ ከሲሪላንካ 25፤ ከኩባ 25 ፤ከኮሎምቢያ 20፤ ከሃይቲ 18፤ ከሩዋንዳ 18 ፤ እንዲሁም ከኡዝቤክስታን 18 ጋዜጠኞች ባለፉት 10 ዓመታት አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን አስታዉቋል።
ሲፒጄ ባወጣው በዚሁ ሪፖርቱ በተለያዩ አገሮች ለጋዜጠኞች ለስደት መዳረግ ዋነ ዋናዎቹ ምክንያቶች የሃይል ጥቃት፤ እስርና እንግልት መሆናቸውን አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም ሲል ሲፒጄ በ2007 ባወጣው መግለጫ ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ቁጥር አንድ የሚዲያ ጠላት እንደሆነ መግለጹ የሚታወስ ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ወያኔ የአሜሪካና የጀርምን ድምጽ ሬድዮ ጣቢያዎችን፤ የግንቦት ሰባትንና የሌሎች ተቃዋሚ ደርጅት ሬድዮ ጣቢያዎችንና አንዲሁም በቅርቡ የተቋቋመዉን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዢን የአየር ላይ ሞገዶችን በከፍተኛ ዋጋ ከቻይና በተገዛ መሳሪያ እንደሚያፍን ታዉቋል።