የፓን ጊ ሙን ድጋሚ መመረጥና አፍሪቃ

ፓን ትልቁን አለም አቀፍ ድርጅት የመምራት ብቃትና ቅልጥፍናቸዉ ብዙ እያስተቻቸዉ ነዉ።በተለይ ለአፍሪቃ መሥራት የሚገባቸዉን ያሕል አልሰሩም የሚል ወቀሳ ይሰነዘርባቸዋል።ያም ሆኖ በድጋሚ ለመመረጥ ከሐያላኑ መንግሥታት ሙሉ ድጋፍ ነበር ያገኙት።