በተጠናቀቀ ሕንፃ ውስጥ ያለፈቃድ ሥራ መሥራት እንደማይቻል ተደነገገ

– የሚኒስትሮች ምክር ቤት የሕንፃ አዋጁን ለማስፈጸም ደንብ አውጥቷል

የሕንፃ ግንባታ የሚያከናውን ማንም ሰው የገነባውን ሕንፃ ካጠናቀቀ በኋላ ሳያሳውቅና ፈቃድ ሳይሰጠው ሥራ ሊጀምር እንደማይችል አዲስ የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ አስታወቀ፡፡