የቅድስት ሥላሴ መ/ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በነገው ክብረ በዓል ችግራቸውን ለምእመኑ ያሰማሉ፤ የቋሚ ሲኖዶሱ አብዛኞቹ አባላት ያለምእመናን ንቅናቄ ችግሩ መፍትሔ እንደማያገኝ ያምናሉ

  • ደቀ መዛሙርቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ቀን የኮሌጁን የምግብ ቤት አገልግሎት ተከልክለዋል
  • የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ደቀ መዛሙርቱ ወደ ክረምት ዕረፍት ከመሄዳቸው በፊት የማጠቃለያ ፈተና እንዲወስዱና ተመራቂዎቹ እንዲሸኙ ጥረት እያደረገ ነው፤ በፓትርያሪኩ የመወሰን አቅም ላይ ጥርጣሬ የገባቸው የሚኒስቴሩ ሓላፊዎች ልዩ ጽ/ቤ ደቀ መዛሙርቱን በኀይል ከኮሌጁ ለማስወጣት ያቀረበውን የድጋፍ ጥያቄ ውድቅ ባደረጉበት አቋማቸው ጸንተዋል
  • ፓትርያሪኩ በሚይዟቸው አቋሞች ረዳት ሊቀ ጳጳሱ አቡነ እስጢፋኖስ ከአቡነ ጢሞቴዎስ ጋራ የእንደራሴነት ሚና እየተጫወቱ መኾኑ እየተነገረ ነው
  • አቡነ ጢሞቴዎስ በኮሌጁ ያላቸው ሥልጣን በግልጽ እንደማይታወቅ ለአጣሪ ኮሚቴው የተናገሩት የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ኮሌጁ ‹‹ጠንካራና ውሳኔ የሚሰጡ የአስተዳደር ሰዎች›› እንደሚያስፈልጉት ጠቁመዋል
  • አጣሪ ኮሚቴው÷ የኮሌጁ አስተዳደር ራሱን ለማረም ዝግጁ እንዳልኾነ ተገንዝቧል፤ ኮሚቴው በየዘርፉ ለታዩ የአሠራር ክፍተቶች በሪፖርቱ ያቀረባቸው የአጭርና የረጅም ጊዜ የማስተካከያ ርምጃዎች በአስቸኳይ ይፈጸሙ ዘንድ የሚመለከተው የበላይ አካል መመሪያ እንዲሰጥበት ጠይቋል