የኮሎኔል ተስፋዬ ወልደሥላሴ ሞት

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

የደርግ የቀድሞ የደህንነት ሚኒስትር፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ወልደሥላሴ፣ ባለፈው ቅዳሜ፣ ግንቦት 27 ቀን 2003 ዓ.ም.፣ በእስር ላይ በነበሩበት ቃሊቲ ወህኒ ቤት አርፈዋል። ወንዳወንድ ገፅታና ደንዳና ሰውነት የነበራቸው ኮ/ል ተስፋዬ፣ በሕይወት ዘመናቸው ብዙ ከመናገር ይልቅ ማዳመጥን የሚወዱ ሰው እንደነበሩ በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ይናገሩላቸዋል። የደርግ አባል አልነበሩም። ሆኖም፣ አብዮቱ የመጣላቸው እንጂ የመጣባቸው እንዳልነበር ነጋሪ አላስፈለጋቸውም። ተስፋዬ የጭቁኖች ልጅ ነበሩ። ወዲያው ነበር ታማኝ የሆኑት።