ፍጥጫና ተቃዉሞ በቱኒዚያ

ትናንት ቱኒዚያ ዉስጥ በፖሊስና በ አንሣር አል-ሻሪያ ቡድን ደጋፊዎች መካከል የተነሳዉ ዉዝግብ የአንድ ሰዉ ህይወት ቀጥፎ ለብዙዎች ጉዳት ምክንያት ሆኗል። ግጭቱ በዋና ከተማ ቱኒዝና አቅራቢያዋ በሚገኙ አካባቢዎችም መዛመቱ ሲገለፅ መንስኤዉ ቡድኑያ ሊያካሂደዉ የነበረዉ ስብሰባ በመንግስት መታገዱ ነዉ።