አፍሪቃና ቴክኖሎጂ

የቴክኖሎጂዉ እድገት የፈጠረዉ ክፍተት ተመራማሪዎች እንደሚሉት ተንቀሳቃሽ ሥልክና ኢንተርነት በአንፃራዊነት በተስፋፋባቸዉም ሐገራት የሚታይ ነዉ።ናይሮቢ-ኬንያ የሚገኘዉ የጥናንት ተቋም ባልደረባ ያስፐር ግሮስኩርት እንደሚሉት ቴክኖሎጂዉ ቢኖር እንኳ አንዳዴ ዉጤቱ መጥፎ ነዉ።