የአዲስ አበባው መንፈሳዊ ኰሌጅ እንደተዘጋ ነው፤ ጉዳዩ ሕግ ፊት ቀርቧል
አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳ ኰሌጅ ተደጋግሞ ሲዘጋና ሲከፈት ቆይቷል።
ከወር በፊት ተማሪዎቹ «ያቀረብነው ጥያቄ እስኪመለስ» በሚል ቢያቋርጡም ፓትርያርኩ «እየተማራችሁ ጥያቄው ይታያል» የሚል መልስና መመሪያም ስለሰጡ ትምህርቱ ተጀመረ።
አሁን የሁሉንም መምህራን ክፍል እየተከታተሉ ነገር ግን እንዲነሱላቸው የጠየቋቸው መምህራን ወደ ክፍል ሲገቡ እየጣሉ በመውጣታቸው፣ አስተዳደሩ «የእነሱን ትምህርት ካልተማራችሁማ እዘጋዋለሁ» ብሎ መጋቢት 30 ቀን «ኰሌጁ ከዛሬ ጀምሮ ተዘግቷል» የሚል ማስታወቂያ ለጠፈ።
አሁን ድረስ ኰሌጁ እንደተዘጋ ሲሆን፣ ተማሪዎቹም ያለ ምግብ እየተራቡ መቀጠል ስላቃታቸው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል።
ፍርድ ቤቱም «የተወሰኑ ተማሪዎች ወክሉ እንጂ ሁላችሁም …