በገደብ የተነሳው የሶማሊያ የጦር መሳሪያ ሽያጭ ማዕቀብ

አዲሱ የሶማሊያ መንግሥት ባቀረበው ጥያቄ ና አሜሪካንም በሰጠችው ድጋፍ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በሶማሊያ ላይ የጣለውን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ማዕቀብ ከትናንት በስተያ ለአንድ አመት እንዲነሳ ወስኗል ። ማዕቀቡ መነሳቱ የሶማሊያ ጦር እንዲጠናከር ያደርጋል።