የልጆቼ የጎህዬና የሱመያ፣ የሩቴና የኦማር “ጩኸት”
አብዩ በለው
ዓርብ ሴፕቴምበር 10 ቀን 2010 እ.ኤ.አ. ከሌሊቱ ለሰባት ሰዓት አስር ጉዳይ (12:50 AM) በኢሜል ለማገኛቸው የትየለሌ ወዳጆቼ ለ2003 ዓ.ም. የአዲስ አመት መልካም ምኞት መግለጫ የላኩላቸው መልዕክቴ የሚከተለው ነበር።
“መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ! እንኳዋን ከዘመን ዘመን በጤና አሸጋገራችሁ! እኔ ግን ከሃሌ ጋር እንዲህ ብያለሁ። ብርቱን ጥዬ አልሻገርም!”