የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ተመክሮ

«ከውድድሩ ወጥተናል፣ ሆኖም ሰፋ ያለ ተመክሮ አካብተናልና ፣ ከዚህ ልምድ በመነሣት የወደፊቱን ሂደት እንቀይሳለን» ። ይህን ያሉት ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አቶ ሰውነት ቢሻው ናቸው። ከ 31 ዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪቃ የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ብቅ ያለውና በመጀመሪያ ዙር ተሸንፈው መውጣት ዕጣቸው ከሆነ 8 የአፍሪቃ ሃገራት ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን፣ በደቡብ አፍሪቃ ስላሳየው እንቅሥቃሴ፤ ስለደጋፊዎቹም አስተዋጽዖ፤ ሃይማኖት ጥሩነህ ከደቡብ አፍሪቃ ፣ የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅራ ልካልናለች። ያዳምጡ: