አያት አክሲዮን ማኅበር የመከላከያ ምስክሮቹን ማሰማት ቀጥሏል

በታምሩ ጽጌ እና በለምለም ፀጋይ

የአያት አክሲዮን ማኅበር ዋና ባለድርሻና ሥራ አስኪያጁ አቶ አያሌው ተሰማ፣ ዶ/ር መሐሪ መኮንንና አቶ ጌታቸው አጐናፍር መጋቢት 29 ቀን 2003 ዓ.ም. ካቀረቧቸው አምስት የመከላከያ ምስክሮች አራቱን አሰሙ፡፡