የአፍሪቃ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር

ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ የሚካሄደው 29ኛው የአፍሪቃ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በፊታችን ቅዳሜ ይጀመራል። በጆሃንስበርጉ የዓለም ዋንጫ ስታዲዮም ጨዋታውን የሚከፍቱት አስተናጋጇ አገር ደቡብ አፍሪቃና ካፕ ቬርዴ ናቸው።