የኢትዮጵያውያን ግጭት በሳውዲ

በዋና ከተማዋ በሪያድ ና በሌሎችም ከተሞች በሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካከል የሚነሳው ግጭት አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ኢትዮጵያውያን ነዋሪዎች አስታወቁ ። ነዋሪዎች ለዶቼቬለ እንደተናገሩት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳውዲ የሚገቡ ኢትዮጵያውያን በብሔር ተከፋፍለው እንዲሁም በቂም በቀል በሚፈጥሩት ግጭት ለሞት ለከፋ የአካል ጉዳት እየተዳረጉ ነው ።