የቀድሞው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተከላከሉ ተባሉ
በታምሩ ጽጌ
የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ሥልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም ሙስና ፈጽመዋል በሚል በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል፣ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ይዞ በመገኘት የሙስና ወንጀልና ትክክለኛ ያልሆነ የምዝገባ መረጃ የመስጠት ወንጀል ክስ የመሠረተባቸውን፣ በሰነድና በምስክሮች በማስረዳቱ የቀድሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች እንዲከላከሉ ከትናንት በስቲያ ብይን ተላለፈባቸው፡፡