ያለውጤት ያበቃው የሱዳኖች ድርድር

የሁለቱ ወገኖች ድርድር በተለይ ባለፈው መስከረም የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሽርና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር አዲስ አበባ ውስጥ የተፈራረሙት ስምምነት ተግባራዊ በሚሆንበት መንገድ ላይ ነበር ያተኮረው ። ይሁንና ተደራዳሪዎቹ ሳይግባቡ በያዙት የማይታረቅ አቋም መለያየታቸው ተዘግቧል ።