በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአንድነት ልዩ አስተባባሪ ኮሚቴ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ሊያደርግ ነው

–    ዶክተር ኃይሉ አርዓያ ከኃላፊነታቸው ተነሱ

በታምሩ ጽጌ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልዩ አስተባባሪ ኮሚቴ በአገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ታህሳስ 14 ቀን 2005 ዓ.ም. ውይይት እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡