የጂማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጥያቄ፣ የአስተዳደሩና የኅብረታቸው ምላሽ

ጂማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትናንት ተፈጥሯል በተባለ ችግር ከፖሊስ ጋር ግጭት እንደነበረ አንዳንድ ተማሪዎች ሲገልፁ የተፈጠረ ግጭትም ይሁን የተጎዳ ተማሪ አለመኖሩን የተማሪዎቹ ኅብረት ፕሬዚዳንት እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ለቪኦኤ ገለፁ፡፡