የሩዋንዳ ልማት የገንዘብ ተቋም

ገና ከጅምሩ በመዋጮ ማሰባሰቡ ዘመቻ ላይ ትችቶች እየተሰነዘሩ ነው ። መገናኛ ብዙሃን እንደሚሉት መዋጮው ሁልጊዜም በፈቃደኝነት አይደለም የሚሰጠው ። ሃብታም ሩዋንዳውያን ከገቢያቸው 10 በመቶ እንዲያዋጡ ይጠበቃል ። ከዚህ ሌላ በዚህ መዋጮ የማይሳተፉት የሚገጥማቸው ማህበራዊ ጫናም ከፍተኛ መሆኑን ነው ታዛቢዎች የሚናገሩት ።