የማይተላለፉ በሽታዎች

ከሰዉ ወደሰዉ የማይተላለፉ በሽታዎች ትኩረት እንደተነፈጋቸዉ የህክምና ባለሙያዎች አዘዉትረዉ ይጠቁማሉ። እንዲህም ሆኖ ከእነዚህ በሽታዎች መካከል በተለይ ኢትዮጵያ ዉስጥ የልብ ህመም፤ የደም ብዛት እንዲሁም የስኳር በሽታ ከፍተኛ ትኩረት ሲያገኙ ካንሰርን በሚመለከት ህብረተሰቡ ዝምታን እንደሚመርጥ ነዉ የሚነገረዉ።