የሙስሊሞች እንቅስቃሴ ክፍል 2 – ምላሽ ለዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

አማኑኤል ዘሰላም

መግቢያ

አንባቢያን ሰፊ ግንዛቤ ይኖራቸው ዘንድ፣ የሙስሊም አክራሪነት እንዴትና ከየት እንደተጀመረ፣ በአሁኑ ወቅትም በአለማችን ምን አይነት ችግር እያስከተለ እንዳለ ለማሳየት ሞክሪያለሁ። በተለይም ሳውዲ አረቢያ፣ ካላት የነዳጅ ክምችት የተነሳ በምታገኘው ፔትሮ ዶላር፣ ምን ያህል፣ ለሰብዓዊነት ክብር የሌለውን አክራሪነት ለማስፋፋት የምትጫወተው አሉታዊና ሰይጣናዊ ሚና፣ የማያሻሙ መረጃዎች በማስቀመጥ ግንዛቤ እንዲኖር ለማድረግ ሞክሪያለሁ። በክፍል ሁለት ትኩረቴን በውጭ አገራት ካሉ የአክራሪነት እንቅስቃሴዎች አንስቼ በአገራችን እየታዩት ወዳሉት የሙስሊም እንቅስቃሴዎች እዞራለሁ።