መኢአድ በገዢው ፓርቲ ላይ የሰነዘረው ወቀሳ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፡ መኢአድ፡ በአባሎቹ ላይ የቀጠለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ እንዲቆም ዛሬ ባወጣውና በአዲስ አበባ ለሚገኙ ኤምባሲዎች፡ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ባሰራጨው መግለጫ ጠየቀ።