የኢትዮጵያውያን አይሁዳውያን የእሥራኤል ጉዞ

እሥራኤል በኢትዮጵያ የቀሩትን የመጨረሻዎቹን የቤተ እሥራኤላውያን ወገኖችን በጠቅላላ በቅርቡ ወደ ሀገርዋ እንደምትወስድ አስታወቀች። በዚሁ መሠረት እሥራኤል ባነቃቃችው «የርግብ ክንፍ» በተሰኘው ዘመቻዋ ከጎንደር ከመጨረሻዎቹ የመጀመሪያዎቹን ኢትዮጵያውያን ቤተ እሥራኤላውያን በሣምንቱ መጀመሪያ ወደ ቴል አቪቭ እንዲገቡ አድርጋለች።