የአጥቢያ ኮከብ አቶ አህመዲን መሃመድ ናስር

“ማንበብ ምርጫ አይደለም ግዴታ ነዉ” ይላሉ የቪኦኤ የአጥቢያ ኮከብ እንግዳ አቶ አህመዲን መሃመድ ናስር።  አቶ አህመዲን ለአንድ ሃያ ዓመታት አሜሪካ ዉስጥ በኦክላንድ ካሊፎርኒያ ኖረዉ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱ አገር ወዳድ ናቸዉ።

የአሜሪካ ኑሮ ቢመቸኝም ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት ለወገኖች ያለኝን የማበርከት አላማ ስላለኝ ነዉ ብለዋል። ስለዚህም ኢትዮጵያ ዉስጥ በቆዩበት አራት ዓመታት አስር ቤተ መጽሐፍቶችን በሱሉልታ፣ በወልቂጤ፣ በደብረዘይት፣ ደጀን ጎጃም፣ በወልዲያ ወሉ፣ በአዲስ አበባ ላፍቶ ክፍለ ከተማና በካራ ቆሬ በነጻ ከፍተዉ ለሕዝብ አበርክተዋል።

​​​​​​

  ይህንኑ ነጻ አስተዋጽኦ ለማበርከት ደፋ ቀና ሲሉ የገጠማቸዉን የቢሮክራሲ ችግር “ብረር ብረር የሚያሰኝ ነዉ” ነገር ግን በአንድ ወቅት ፕሬዚዳንት ኬኔዲ እንደተናገሩት ”እኛ ካልሆንን ማን? ዛሬ …