ለመንግሥት “ማስጠንቀቂያ” እየሰጠን ነው ያሉ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አደባባይ ዋሉ

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዕሁድ መስከረም 27 ቀን 2005 ዓ.ም የሚካሄደውን የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ በመቃወም ዓርብ መስከረም 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ በዋና ከተማይቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ውስጥ ተቃውሞ አሰምተዋል።