ሽልማት ለዴዝሞን ቱቱ

ሞ ኢብራሂም የተሰኘዉ ተቋም ለደቡብ አፍሪቃዊዉ የፀረ አፓርታይድ ታጋይ ሊቀ ጳጳስ ዴዝሞን ቱቱ ልዩ ያለዉን ሽልማት እንደሚሰጥ አስታወቀ። ተቋሙ ሽልማቱ ሊቀጳጳሱ በዘመናቸዉ ላበረከቱት አስተዋፅኦና በኃያላን ፊት እዉነቱን ለመናገር በመድፈራቸዉ መሆኑን አመልክቷል።