ቪቫ ስዬ አብርሃ!
ያሬድ አይቼህ
በሚኒሶታ ከተማ የአቶ ስዬ አብርሃንና የፕ/ር መረራ ጉዲናን ንግግሮች ፓልቷክ ዱቅ ብዬ ሰማሁ። ሁለቱም የዴሞክራሲ ታጋዮች ያቀረቡዋቸው ነጥቦች ግሩም ናቸው። በተለይ አቶ ስዬ ከስብሰባው ታዳሚዎች አንዱ ከነበሩት ከአቶ ጌዲዮን የቀረበላቸውን ጥያቄ አስከትለው ያነሱዋቸው ጉዳዮች እጅግ በጣም ማረኩኝ። ለካስ የበሰሉ የፓለቲካ ታጋዮች ኢትዮጵያ አፍርታለች! አቶ ስዬ አብርሃ በአንድ ጎኑ ብቻ የበሰለ ሰው አይደሉም። አቶ ስዬ በሁለቱም ጎኑ ተገላብጦ እንደበሰለ አንባሻ ናቸው።