የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አመታዊ ጉባኤ

በሶሪያ ጉዳይ ግራ ቀኝ የቆሙት ሐያላን መንግሥታት ግን ያኔም-አሁንም እንደተወዛገቡ ነዉ።ዛሬ የሚጀመረዉ ጉባኤ ሞስኮና ቤጂንግን ባንድ ወገን፥ ዋሽግተን፥ ለንደንና ፓሪስን በተቃራኒዉ ላቆሙዉ ለሶሪያ ጦርነት ሁነኛ መፍትሔ መጠቆሙ አጠራጣሪ ነዉ።