ፍቼ – ጨምበላላ፣ እሥራቶች፣ ሲአንና የዞኑ አስተዳደር

አባሎቹና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች በተለያዩ የሲዳማ ዞን ወረዳዎች ውስጥ እየታሠሩ እንደሚጉላሉ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ አስታወቀ፤ የታሠሩት በሕገወጥ ተግባር ላይ በመሠማራታቸው ነው ሲል ዞኑ ይናገራል፡፡