ኪስማዩና የሶማሊያ ተፋላሚ ኃይሎች

የሶማሊያው ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ ከመቅዲሾ በስተደቡብ ከምተገኘዋ ከኪስማዩ ካፈገፈገ ቀናት ተቆጥረዋል ። ይሁንና ከተማይቱ እስከ ዛሬ በአፍሪቃ ህብረት ኃይል በሚደገፈው በሶማሊያ መንግሥት ወታደሮች እጅ አልገባችም ። የመቅዲሾ የዶቼቬለ ወኪል አዌስ ሁሴን እንዳለው አሁን በከተማይቱ የአስተዳደር ክፍተት ተፈጥሯል ።