‹‹ዳገቱ መሀል ላይ ማረፍም ሆነ መቀመጥ አይፈቀድልንም›› ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

በጋዜጣው ሪፖርተር

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን በቅርቡ እንደሚተኩ የሚጠበቁት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሰኞ ምሽት ለሕዝቡ ምሥጋና ለማቅረብ ባደረጉት ንግግር፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕልፈተ ሕይወት ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ላሳየው ጨዋነት የተሞላበት የሐዘን ሥርዓት በመንግሥትና በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ስም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡