ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ዛሬ ሌሊት ዐረፉ

                            ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ዐርፈዋል፡፡

እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር

ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናትና ምእመናን ይህ ነገር በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ያልታሰበ አደጋ እንዳያመጣ ጥንቃቄ የተሞላ ሃይማኖታዊና ጥበባዊ ሥራ መሥራት አለባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ አራት ነገሮች እንዳይፈጠሩ ጥንቃቄ ያስፈልጋል

  1. የእርሳቸው ደጋፊና ተቃዋሚ በሆኑ አካላት መካከል በሚፈጠር ግጭት ቤተ ክርስቲያኒቱ እንዳትታወክ
  2. ሀብት እና ቅርስን የማሸሽ አዝማሚያ እንዳይከሰት
  3. ቤተ ክርስቲያኒቱን ማን ለጊዜው ይምራት በሚለው ዙርያ በሚፈጠረው ልዩነት አደጋ እንዳይከሰት
  4. በቀጣይስ ማን በወንበሩ መቀመጥ አለበት በሚለው ዙርያ ችግር እንዳይከሰት
አሁን የመረጋጊያ ጊዜ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ምንም ዓይነት ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ለፓትርያርኩ የኀዘን ጊዜ ያውጅ፡፡ ጊዜያዊ ኮሚቴ ያቋቁም፡፡ ነገሮችን በግልጽነት ለሕዝቡ ይፋ ያድርግ፡፡ ከግብጽ ቤተ ክርስቲያን ልምድ ይውሰድ፡፡ ማንኛውም የፓትርያርኩ ንብረቶች ወደ ሌሎች ከመጓዛቸው በፊት በጥብቅ ይቀመጡ፡፡ የባንክ ሂሳቦች ይዘጉ፡፡
አሁን የመረጋጊያ ጊዜ ነው፡፡ ለሀገሪቱም ሆነ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሲባል ቤተ ክርስቲያኒቱን በዚህ ሁኔታ ወደ ጸጥታ ወደብ የሚመራ አመራር ያስፈልጋል፡፡
ዝርዝሩን እንመለስበታለን፡፡