ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ስንብት የሦስት ቀናት ልዩ ፕሮግራሞች ተዘጋጁ

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብሔራዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት የፊታችን እሑድ ነሐሴ 27 ቀን 2004 ዓ.ም. በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ታወቀ፡፡