ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በደቡብ አፍሪቃ

በደቡብ አፍሪቃ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በፖሊሶች እንደሚሳደዱ እና እንደሚዘረፉ ዛሬ ለዶቼቨለ አማርኛው ክፍል ገለፁ። የደቡብ አፍሪቃ ፖሊሶች በፈረሶች ላይ ሆነው በውሾች ጭምር በመታገዝ እያሳደዱ እንደሚይዟቸውና ገንዘብ እንደሚወስዱባቸው ስደተኞቹ ተናግረዋል።