የእሁዱን የሕዝበ ሙስሊም ስብሰባ ወያኔ ሕገወጥ ነው አለ
ሐይማይኖትን ሽፋን ያደረጉ አንዳንድ ወገኖች የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ስብሰባ በሚካሄድበት ቀን የተከለከለና ሕገወጥ ስብሰባ ለማድረግ እየተዘጋጁ ነው ሲል ፌደራል ፖሊስ አስጠንቅቋል፡፡
በሌላ በኩል ግን በአዲስ አበባ መስጊዶች የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ወይም ሰደቃ ለማድረግ ዕሁድ ሐምሌ ስምንት ቀን የተያዘው የሙስሊም አማኒያን ፕሮግራም ሠላማዊ ነው፤ የሐይማኖት ጉዳይ ነው፤ በታሰበው መሠረት ይካሄዳል ሲሉ የሕዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ከሚል ሸምሱ ለቪኦኤ አመልክተዋል፡፡
የመንግሥትን ማስጠንቀቂያ የሚመለከተውን ዘገባና ከአቶ ከሚል ሸምሱ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለምልልስ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ፡፡