ኳስና ቅሪላ፤ ሆድና ሕሊና
ከቴድሮስ ሐይሌ
‘’መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው፥ መጨረሻቸው ጥፋት ነው ።’’ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፥19
ዋሽቶ ለመኖር ልቤ አይችልም ከቶ፤
ታምኖ ይኖራል እንጂ ያለውን በልቶ።
ደልቶኝ የሞላ ኑሮ መኖር ባልጠላም፤
ይህን ለማግኘት ብዬ እኔ አላጣም ሰላም ።
…ሕሊና ሲያጣ ሰላም ወርቅ አልማዝ ሞልቶ ፤
ሳይተኙ መኖር ሊኖር ከራስ ተጣልቶ ፤
አስኮንኛት ነብሴን እኔ አልሞላም ኪሴን!!!
በሙያው የህዝብ ልጅነትን ከእድሜው በላይ መከበርን በሚሊዮኖች መፈቀርን በህፃን በአዛውንቱ መወደስን የተቸረው ብላቴናው የሙዚቃው ኮከብ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከዚህ በላይ የቀረበውን ስንኝ ያዘለውን አስተማሪ መንፈሳዊና መካሪ በሆነው በዚህ ዘፈኑ ላይ በሐሰት ከሚገኝ ገንዘብ ይልቅ የሕሊና ሰላም ምንኛ የተሻለ እንደሆነ ያሳየበት ከቤተመንግስቱ እስከ ቤተክህነቱ በንዋይ ፍቅር የእውነትን ዋጋ በሚያቃልሉበት ሃብት ሞልቶ የተተትረፈለት ከበርቴ ከረሐብተኛ ሕዝብ መከራ ላይ የበለጠ ትርፍ ለማጋበስ ከማፍያና ወንጀለኛ አገዛዝ ጋር ተባብሮ ወገኑን ሲያስጨቁን የሚታይበትን ‘’ምን አይነት ዘመን ነው የተገላቢጦሽ አህያ ወደ እርሻ ውሻ ወደ ግጦሽ ‘’ አበው እንዲሉ የኛ የኢትጽያውያን ሁኔታ እንደምሳሌው እየሆነ ያ የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ በሚል ከባድ የቃልኪዳንን አክባሪ ከነበረ ማሕበረሰብ የፈለቀ ወገን….. ይህን ጽሁፍ በPDF ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ