ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በግብፅ

በግብፅ ለበርካታ ዓመታት በአምባገነንነት የቆዩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ በአደባባይ ተቃውሞ ከስልጣን ከተወገዱ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በኋላ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተከናውኗል። ይህ ምርጫ ግብፃውያን በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ይበጀኛል የሚሉትን ፕሬዚዳንት በነፃነት ለመምረጥ ድምፅ የሰጡበት እንደሆነም ተዘግቧል።