ተቀናቃኝ ቡድኖችና ፖለቲካ

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
ተመስገን ደሳለኝ በተቀናቃኝ ቡድኖች ላይ አዲስ የመነጋገሪያ ርእስ ከፍቶአል (ግንቦት 3፣ 2004)፤ ጉዳዩ በጣም አንገብጋቢና በጣም ወቅታዊ ነው፤ እንደተለመደው አንብበን ችላ የምንለው ጉዳይ አይደለም፤ ሁላችንም በተቻለን መጠን እውነትን ይዘን ያለ ይሉኝታና ያለፍርሃት በራሳችን ላይ እንዝመትና እውነትን ይዘን እንነሣ።