እየተረጋጋ ነው

በአሁኑ ሰዓት በዝቋላ ገዳም ነገሮች እየተረጋጉ ነው፡፡ ወደ ገዳሙ የሚወጣው ሕዝብ በመብዛቱ የተነሣ በአካባቢው የጸጥታ አስከባሪዎች እና በተጓዡ መካከል ተፈጥሮ የነበረው አለመግባባት በአሁኑ ጊዜ የረገበ ሲሆን የጸጥታ አስከባሪዎች ወደ ቦታው የሚሄደው ሕዝብ ከበዛ ለመስተንግዶ እና ቁጥጥር ሊያስቸግር እንደሚችል ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡