የዓመቱ የመፃፍ ነፃነት ተሸላሚ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

ዓለም አቀፉ የፔን – አሜሪካ ተቋም በእስር ላይ የሚገኘውን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የአመቱ የመፃፍ ነፃነት ተሸላሚ አድርጎ መርጧል። ኢትዮጵያ ውስጥ በፀረ ሽብር ስም የመፃፍ ነፃነት ላይ ጫና እየተፈጠረ ነው ያለው ድርጅቱ እስክንድር የደረሰበትን ጫና ሁሉ ተቋቁሞ የመፃፍ ነፃነትን መብት ለማስከበር ባደረገው ትግል ለዚህ ሽልማት መመረጡን አውስቷል። የዋሽንግተን ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀ ዝርዝር ዘገባ ይዟል።

[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/F47128AD_1_dwdownload.mp3[/podcast]