የባሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አረፉ
(ደጀ ሰላም)፦ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ፣ የባሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ዛሬ የካቲት 24 ቀን 2003 ዓ.ም አረፉ። የባሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና አሁን ደግሞ በሥራ ላይ የሚገኘው የቋሚ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብፁዕነታቸው ዛሬ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከሰዓት በኋላ ማረፋቸው ታውቋል። በቤተ ክርስቲያን የዕለቱን ሥርዓተ ቅዳሴ ተካፍለው በደህና የተመለሱት ብፁዕነታቸው በድንገት ማረፋቸው የታወቀ ሲሆን መንስዔው ከልብ ጋር የተገናኘ ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮቻችን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው ያረፉት በአዲስ አበባ ነው። ዝርዝሩን እንደደረሰልን እናቀርባለን።