በርታ የሊዝ ገንዘብ ለመክፈል የአዲስ አበባ አስተዳደርን እየተማፀነ ነው

– የሪል ስቴት ግንባታ እንዳያካሂድ ታግዷል

በውድነህ ዘነበ

ላለፋት 40 ዓመታት በግንባታ ኢንዱስትሪ ውስጥ የቆየው በርታ ኮንስትራክሽን ኩባንያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሊዝ ክፍያ ገንዘብ እንዲቀበለው እየተማፀነ መሆኑን ገለጸ፡፡