የአሜሪካን ጦር ከኢራቅ መውጣት ያሳደረው ስጋት

ከሰባት ዓመት በላይ ኢራቅ ከቆዩት የአሜሪካ ተዋጊ ጦር ኃይል አባላት የመጨረሻዎቹ ትናንት ኢራቅን ለቀው ወጥተዋል ። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢራቅ ጦርነት ማብቃቱን ትናንት በይፋ አስታውቋል ።

በርካታ ኢራቃውያን የአሜሪካን ጦር ሀገራቸውን ለቆ በመውጣቱ የተቀላቀለ ስሜት ነው ያደረባቸው ። በአንድ በኩል ሀገሪቱን በኃይል የያዘው የአሜሪካን ጦር በመውጣቱ ደስተኞች ናቸው ። በሌላም በኩል የፀጥታው ሁኔታ ከቀድሞው እጅግ ይባባሳል ብለው መስጋታቸውም አልቀረም ። የዶይቼቬለው ራይነር ዞሊሽ እንደሚለው የአሜሪካን ሠራዊት ኢራቅን ለቆ ከወጣ በኃላ የኢራቅ ፀጥታ ተረጋግቶ መቀጠሉ ለብዙዎች ኢራቃውያን አስተማማኝ አይደለም ።

ዘገባውን ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ፤ [podcast]http://dw-world-od.streamfarm.net/Events/podcasts/amh/4347_podcast_amh_nachrichten/011f4982-podcast-4347-5930519.mp3[/podcast]