አጀንዳ ነጠቃ ከባንዲራው ጀርባ?

የባንዲራው ቀን አከባበር እና ዙሪያውን የሚከተሉትን ንግግሮች ለሚተነትን ታዛቢ ኢሕአዴግ ቢያንስ በዚህ ጉዳይ “የቀኞቹን” አጀንዳ ማንሳቱ መሠረታዊ ሽግሽግ መሆኑ የሚያሻማ አይደለም። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነት አቀንቃኙን አንድ “ትልቅ” አጀንዳ የሚያሳጣው ነው። እርግጥ ቀደም ሲል እንዳልኩት የባንዲራን ጉዳይ ሁሉም ወገን የሚስማማበት ቢሆን አገረዊ ጠቀሜታው የላቀ በመሆኑ የሚደገፍ ነው። በፓርቲ ፖለቲካ ግን “የአጀንዳው አቀንቃኝ እኔ ነኝ፤ ኢሕአዴግ ደግሞ ተቃዋሚ ነው” በማለት ጉዳዩን አጀንዳ አድርጎ ለቆየው ጎራ ፖለቲካዊ ዋጋ የሚያስከፍለው ነው።
ጥያቄዬ ይህ ጎራ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ተረድቷል ወይ የሚል ነው። ሌላው ቢቀር ኢሕአዴግ አጀንዳውን መጋራቱን ሳይነቅፍ ፖለቲካዊ ነጥብ ለማስቆጠር እንደሚችል ወይም ይችል እንደነበር ያውቃል ወይ? ወይስ ኢሕአዴግ አሁን ቢሆን “ባንዲራው ይወክለዋል ለሚባለው ነገር ተግባራዊ ታማኝነት የለውም” ብሎ የሚከራከርበት አጀንዳ አለው? በአርማው ላይ ሕዝበ ውሳኔ ይካሔድ ብሎ መጠየቅ ለዚህ የተሰጠ የታሰበበት መልስ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል?…

በነገራችን ላይ
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲት ንግግር እንዲያቀርቡ የቀረበላቸው ግብዣ እንዳሰቡት አልተሰካም። ጭራሹንም ያልታሰበ ትኩረት ስቦ አሳጣቸው እንጂ። ከንግግሩ በኋላ ወደ መኪናቸው ሲያመሩ አንድ የሚያጽናና ንግግር ለራሳቸው ማድረግ አለባቸው፤ ብቻቸውን….(ለምሳሌ እንዲህ የሚል) ….
ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ