የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ ተጠናቀቀ


  • እነ ንቡረ እድ ኤልያስ በአጣሪ ኮሚቴው ስም ባቀረቡት ሪፖርት ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከሐዋሳ እንዲነሡ፣ በማኅበረ ቅዱሳን የሓዋሳ ማእከል እንዲዘጋ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።
  • ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ጠንካራ ሥራ አስኪያጅ ከሁለት ረዳቶች ጋራ ተመድቦላቸው ባሉበት ሀገረ ስብከት ይቀጥላሉ፤
  • ሦስት የአጣሪ ኮሚቴው አባላት ማኅበረ ቅዱሳንን የቤተ ክርስቲያን ካልሆኑ አካላት ጋራ ደምረው ለመክሰስ ያደረጉትን ሙከራ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ እና ሌሎች ብፁዓን አባቶች ተቃወሙ፤
  • “በሓላፊነቴ የራሴ መረጃ አለኝ፤ ለምንድን ነው ማኅበሩን የችግር ምሕዋር ውስጥ የምትከቱት?” (ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ)
  • በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እና ደቀ መዛሙርት ስም በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የቀረበው የክስ አቤቱታ በኮሌጁ ሊቀ ጳጳስ፣ ምክትል አካዳሚክ ዲን እና ሌሎች ተማሪዎች ተቃውሞ ገጠመው
  • “ፕሮቴስታንታዊውን የተሐድሶ ኑፋቄ ወጥመድ የሚያጋልጠው ሰነድ ሲም የተባለ የተሐድሶ ድርጅት በአጭር ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን ለመውረስ የቴዎሎጂ ት/ቤቶችን ማእከል አድርጎ ለመንቀሳቀስ የያዘውን ዓላማ የሚያጋልጥ እንጂ ኮሌጁን እንደ ተቋም የሚወነጅል እንዳልሆነ በበለጠ ግልጽነት ሊሠራበት ይገባል፡፡”(ብዙኀን የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት)
(ደጀ ሰላም፤ ኤፕሪል 14/2011)፦  በአስቸኳይ የተጠራው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የምልአተ ጉባኤውን ሥልጣን እና ክብር የሚያስጠብቁ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ማምሻውን ተጠናቀቀ፡፡ ከሃያ ያላነሱ አባላት በተገኙበት ረቡዕ ጠዋት በተከፈተው አስቸኳይ ስብሰባ መጀመሪያ ላይ በዐባይ ወንዝ ላይ ለሚሠራው ለታላቁ ሚሌኒየም ግድብ ግንባታ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የአንድ ወር ሙሉ ደመወዛቸውን ለማበርከት ተስማምተዋል፤ በዚህ ረገድ ምእመናን እና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን በቀጣይነት በተለያየ መልክ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ ለማበረታት ተወስኗል፡፡

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)